በነፃነት ፖድካስት ላይ እኛ አዘጋጆቹ ፅላተ እና ጽዮን ከእንግዳችን ማህሌት ጋር ስለ ሴትነት እና ስለ ኢትዮጵያዊ ሴቶች ተጨባጭ ሁኔታ ጥልቅ ዳሰሳ አድርገናል፡፡ ይህ የፖድካስት ክፍል የፊሜኒዝምን መሰረታዊ መርሆችን በጥልቀት የሚያውጠነጥን፤ በማህበራዊ ድህረገፆች ግንዛቤዎችን መስጠት ስላለው ጉልህ ሚና የሚዳስስ እና ኢትዮጲያውያን ሴቶች በየቀኑ የሚያጋጥሟቸውን ውስብስብ ፈተናዎች የሚተነትን ነው፡፡ ፊሜኒዝምን ተከትሎ የሚመጣውን መገለል፤ በግል እና በጋራ የሚገጥሙንን ችግሮች እየጠቀስን፤ በማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አብዛኛዎቹ ሴቶች የሚያጋጥሟቸውን የገቢ ልዩነት፤ የቤት ውስጥ ጥቃት እና የደህንነት ስጋት የመሳሰሉ እውነታዎች በማንሳት እንወያያለን፡፡
ማህሌት ያሏትን ልዩ ልዩ ሀሳቦች እና ታሪኮች ጋር አጋርታናለች፤ ውይይታችን የፆታ እኩልነትን እና የሴቶችን መብት ከማስከበር ያለፈ ገጽታን ያለው ነው፡፡ በዚሁ ክፍል ላይ ሴቶችን የሚያነቃቁ እነ የሚያበረታቱ ስልቶችን እናካፍላችኋል፡፡ ከዚያም በተጨማሪ የማህበረሰብ ድጋፍ እና የባህል ግንዛቤ አስፈላጊነት የሚያመጣውን ለውጥ እየዘረዘርን እንወያያለን፡፡ ይሄ የፖድካስት ክፍል አድማጮች ስለ ፊሜኒዝም ያለውን እውነታ በጥልቀት እንዲረዱ እና በኢትዮጵያ ስለፊሜኒዝም እና ሴቶች ስለማብቃት በሚደረገው ውይይት ላይ እንዲሳተፉ የሚያበረታታ የሃሳብ ልውውጥ መንገድን የሚከፍት እንደሚሆን ይታመናል፡፡ ትርጉም ያለው እና ለውጥን የሚያወጣ ውይይት የተደረገበንበትን ይሄንን ልዩ የነፃነት ፖድካስት ክፍል አሁኑኑ ያዳምጡ!
Instagram: instagram.com/netsanetpodcast
X (formally known as Twitter): twitter.com/NetsanetPodcast
TikTok: www.tiktok.com/@netsanetpodcast
????????Music Credit:
Telegram: t.me/NERLIV
Instagram: www.instagram.com/Nerlivmusic/
YouTube: tinyurl.com/nerlivketero
Become a Teraki subscriber today to get exclusive content! @terakiapp
Thanks for being a part of our podcast family, and we can't wait to share this episode with you! ????️✨
Category : Interviews and Podcasts